Telegram Group Search
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ግንባታን አስጀመሩ‼️

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ይህ ታሪካዊ ክስተት የኢትዮጵያ አዲስ የፈጠራና ከፍተኛ የኢኮኖሚ ልማት ጅማሮን የሚያበስር ነው ብለዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም የኢኮኖሚ ፈጠራን በማራመድ፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማብቃትና ዘላቂነትን በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ይሆናል ነው ያሉት።

የኢኮኖሚ ፈጠራን በማራመድ ረገድ ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ስትራቴጂ የማዕዘን ድንጋይ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አንስተዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
230 ኢትዮጵያውያን ከኦማን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ‼️

ወደ ሀገር ቤት የተመለሱት ዜጎች ሁሉም ወንዶች መሆናቸው ተገልጿል፡፡ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡

ከሚያዝያ 29 ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ በሚገኘው ከኦማን ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ 460 ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

በኦማን የሚገኙ 1 ሺህ 590 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር ለመመለስ መታቀዱ የሚታወስ ነው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
[CREATINE MONOHYADRATE ]

ጡንቻን ለመገንባት እና ጉልበት ለማግኘት፤ ለሰውነትዎ የሚያስፈልገውን ይስጡት!

በፆም ወቅት የሚወሰድ!

ጥንካሬ፣ብርታት እና ፈጣን የሰዉነት ጥገና ያስፈልገኛል ብለዉ ካሰቡ ክሬቲን ይገባዎታል
👨🏾‍⚕️የዘርፉ ባለሙያዎች ጥናት እንደሚያሳየዉ ክሬቲን የሚጠቀሙ አትሌቶች እና ስፓርተኞች 23 % የተሻለ አፈጻጸም እና ጥገና ያሳያሉ!🏃‍♂️

ለነፃ የምክር አገልግሎት እና የተሟላ መረጃ ወደ ጥሪ ማእከላችን ይደውሉልን
☎️9369 ☎️

አድራሻ📍 አዳማ - ፖስታ ቤት ሶሬቲ ህንፃ ፊትለፊት ጀርመን ሲቲ ሞል 1ኛ ፎቅ ሱቅ ቁጥር 110

☎️ +251966113766 ☎️

Join https://www.tg-me.com/+RCaZ_Ka6SOrlz0u5
ፍልስጤም 194ኛዋ የተመድ አባል ሀገር እንድትሆን ድጋፍ አገኘች‼️

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ትላንት አርብ ሲከናወብ የፍልስጤምን የድርጅቱ ሙሉ አባልነት ደግፏል።

143 ሀገራት ለውሳኔ ሃሳቡ ድጋፋቸውን የሰጡ ሲሆን፥ 25 ሀገራት ድምጸ ተአቅቦ አድርገዋል።አሜሪካና እስራኤልን ጨምሮ ዘጠኝ ሀገራት ደግሞ የፍልስጤምን ሙሉ የተመድ አባልነት እንደማይቀበሉት አስታውቀዋል።

የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ትናንት ያሳለፈው ውሳኔ ፍልስጤም በክርክሮች እና አጀንዳ ቀረጻ እንድትሳተፍና በተለያዩ ኮሚቴዎች እንድትወከል ተጨማሪ መብትን የሰጠ ነው።ሙሉ አባልነቷ በጸጥታው ምክርቤት እስካልጸደቀ ድረስ ግን በተለያዩ ውሳኔዎች ላይ ድምጽ መስጠት አትችልም።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
ጎሮ አካባቢ በተከሰተ የእሳት አደጋ 13 የንግድ ሱቆችና በጋራዥ ዉስጥ የነበሩ አምስት ተሽከርካሪዎች ሙሉ በሙሉ ወደሙ‼️

ግንቦት 3 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት 6:50 በለሚ ኩራ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 9 ጎሮ ገብርዔል ቤተክርስቲያን አጠገብ የተነሳዉ የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

በእሳት አደጋዉ በቤተክርስቲን ዙሪያ ያሉ 13 የንግድ ሱቆችና በጋራዥ ዉስጥ የነበሩ አምስት ተሽከርካሪዎች ሙሉ ሙሉ የወደሙ እና በጋራዡ ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል።

የእሳት አደጋዉን ለመቆጣጠር 12 የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪዎች 66 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የተሰማሩ ሲሆን የእሳት አደጋዉን ለመቆጣጠርም 4 :10 ሰዓት መፍጀቱን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች እሳቱን ለመቆጣጠር ባደረጉት ርብርብ እሳቱ ወደ-ቤተክርስቲያኒቱ እንዳይዛመት ማድረግ የቻሉ ሲሆን በጋራዡ የነበሩ ቁጥራቸዉ 15 የሆኑ ተሽከርካሪዎችንም ማዳን ችለዋል።በአደጋዉ በሰዉ ላይ ምንም ጉዳት አልመድረሱን አቶ ንጋቱ ጨምረው ለብስራት ተናግረዋል።

በጋራዡ ውስጥ የነበሩ ተሽከርካሪዎች የያዙት ነዳጅና ሌሎች ፈሳሽ ተቀጣጣዮች እንዲሁም ንግድ ሱቆቹ እሳትን ሊቋቋሙ ከማይችሉ ቆርቆሮና መሰል ግብዓቶች መገንባታቸዉ  ለእሳቱ መባባስ አስተዋጾኦ ማድረጉን አቶ ንጋቱ ተናግረዋል።

የተሽከርካሪ ጥገና አገልግሎት የሚሰጡ ጋራዦች ደረጃቸዉን በጠበቁ ግብዓቶች የተገነቡና ከንግድ ሱቆች ከመኖሪያ አካባቢዎች  የራቁ መሆን እንዳለበት ኮሚሽኑ አስጠንቅቋል።


@Esat_tv1
@Esat_tv1
ጠ/ሚኒስትሩ እና ርዕሰ መስተዳደሩ በመሳሪያ የተደገፈ ትግል ለሚያካሂዱ የአማራ ክልል ታጣቂዎች "መገዳደል ይብቃን" ሲሉ ጥሪ አቀረቡ‼️

ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ በአማራ ክልል መሳሪያ አንግበው ትግል ላይ የሚገኙ ሃይሎች “ትጥቃቸውን ፈትተው በሳላማዊ መንገድ ኑ እና ታገሉ፣ መገዳደል ይብቃን” የሚል ጥሪ አቀረቡ።

ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ “ጫካ ለሚገኙ ወንድሞቻችን” ሲሉ መሳሪያ አንግበር በክልሉ ለሚንቀሳቀሱ ሀይሎች ባቀረቡት ጥሪ “ዛሬ አማራ መሪ አግኝቷል አረጋ ከበደን የመሰለ ታማኝ፣ ትጉህ መሪ አግኝቷል” ሲሉ በማወደስ “ለአማራ መብት የሚታገል ግለሰብም ይሁን ቡድን ከአረጋ አመራር ስር ሁኖ ክልሉን እና ህዝቡን መጥቀም ስለሚችል መገዳደል ይብቃን” ሲሉ አሳስበዋል።

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ለጠ/ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) ምሥጋና ባቀረቡበት መልዕክታቸው “በጫካ ለምትገኙ ወንድሞቻችን” ሲሉ በመጥራት “በእውነት ከክልላችን ሕዝብ ጥቅም እና ክብር ውጭ ሌላ ስውር አጀንዳ ከሌላችሁ በስተቀር ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ.ር) ባቀረቡላችሁ ጥሪ መሠረት ችግሮቻችንን በውይይት እና በድርድር እንድንፈታና ሕዝባችንም እፎይታ እንዲያገኝ በድጋሜ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ” ብለዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
ከሐዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረዉ አዉሮፕላን ዉስጥ ታይቷል የተባለዉ ጭስ በዉስጡ ያለዉ ዘይት በመቃጠሉ የተነሳ መሆኑ ተገለፀ‼️

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሰሞኑ በአዉሮፕላኑ ላይ የተከሰተው ጉዳይን አስመለክቶ እንዳስታወቀው ከእሳት ወይም ከሌላ ነገር ጋር የተያያዘ ሳይሆን አዉሮፕላን ዉስጥ ያለዉ ዘይት ተቃጥሎ ነዉ በወቅቱ የተከሰተው ጭስ ሊፈጠር የቻለዉ ይህም አልፎ አልፎ የሚያጋጥም ችግር ነዉ ብሏል።

የአየር መንገዱ ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰዉ በተለይ ለካፒታል እንደተናገሩት " በአዉሮፕላኑ ዉስጥ ያለዉ ዘይት መጋጠሉ እና ከእርሱ ጋር ተያይዞ የተፈጠረ ጭስ ነዉ ይህ ደግሞ የተለመደ ነዉ ብለዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET154 ሚያዝያ 29፣ 2016 ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ በአውሮፕላን ውስጥ ጭስ መታየቱን አስታዉቆ እንደነበር ይታወቃል ።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ረቂቅ አዋጅ ጸደቀ‼️

ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 26ኛ መደበኛ ስብሰባው አዲሱን የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ አጽድቋል፡፡

የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ የውሳኔ ሃሳቡን ለምክር ቤቱ በንባብ ያቀረቡ ሲሆን ፥ የረቂቅ አዋጁን መሻሻል አስፈላጊነት እና በምርመራው ሂደት የተከናወኑ ተግባራትንም በዝርዝር ለጉባኤው አስረድተዋል፡፡

አዋጁ የአርሶና አርብቶ አደሩን እና ከፊል አርብቶ አደሩን የኑሮ ደረጃ ሀገሪቱ ከደረሰችበት ዘርፈ ብዙ እድገት ጋር እኩል ለማራመድ የሚያስችል መሆኑ መገለጹን ከምክርቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ረቂቅ አዋጁ የተፈጥሮ ሃብቶችን በዘላቂነት በመጠበቅና በማልማት ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ፣ የሴቶች፣ ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞችና ድጋፍ የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመሬት ተጠቃሚነት መብት ማረጋገጥ የሚያግዝ መሆኑም ተመላክቷል፡፡

ረቂቅ አዋጁ በምክርቤት አባላት ሰፊ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ምክር ቤቱ ረቂቅ አዋጁን አዋጅ ቁጥር 1324/2016 አድርጎ አፅድቆታል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
በጅግጅጋ ከተማ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ተመረቀ‼️

በጅግጅጋ ከተማ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ ተመርቆ ስራ ጀምሯል።በ250 ሚሊየን ብር ካፒታል የተከፈተው ፋብሪካው በቀን እስከ 10 መኪኖችን የመገጣጠም አቅም እንዳለው ተገልጿል።

ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ ፋብሪካውን መርቀው በከፈቱበት ወቅት እንዳሉት በክልሉ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ ይገኛል።

ፋብሪካው ለዜጎች የስራ እድል ከመፍጠር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ወጪን በመቀነስ ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ጠቁመው የክልሉ መንግስትም ለግሉ ዘርፍ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥል ብለዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
የፕላስቲክ አምራቾች የወረቀትና የጨርቅ ከረጢቶችን በአፋጣኝ ማምረት እንዲጀምሩ ማሳሰቢያ ተሰጠ‼️

አካባቢን ሊበክሉ የሚችሉ ስስ ፕላስቲኮችን የሚያመርቱ ድርጅቶች የአካባቢ ብክለትን የሚቀንሱ የወረቀትና የጨርቅ ከረጢቶች በአፋጣኝ ማምረት እንዲጀምሩ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አሳሰበ፡፡

ፕላስቲክ በማምረት የተሰማሩ ድርጅቶችና ባለቤቶች ከተፈቀደላቸው 0.03 ማይክሮ ሜትር በታች ሲያመርቱ ከተገኙ፣ ከመዝጋታቸው ባሻገር፣ ከሦስት ዓመት እስከ አሥር ዓመት የእስር ቅጣት እንደሚያስከትልባቸው ሪፖርተር አስነብቧል።

በተጨማሪም ለኅብረተሰቡ ዳቦ የሚያከፋፍሉና ሌሎች ሸቀጦችን በፕላስቲክ ምርቶች ጠቅልለው የሚሸጡ ቸርቻሪዎችም ሆኑ አከፋፋዮች፣ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ይደረጋል ተብሏል።

ሸማቾች ማንኛውንም ዕቃ ሲሸምቱ የፕላስቲክ ውጤቶችን ከመጠቀም ይልቅ፣ ከወረቀትና ከጨርቅ የተሠሩትን መጠቀም ይገባል በማለት ባለስልጣኑ አመልክቷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
ኢትዮጵያ የራሷ የኮሙዩኒኬሽን ሳተላይት ባለቤት እንድትሆን የአዋጭነት ጥናት ተጠናቋል‼️

🗣የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት

ኢትዮጵያ የራሷ የኮሙዩኒኬሽን ሳተላይት ባለቤት እንድትሆን የአዋጭነት ጥናቱ ተጠናቆ ለሚመለከተው የመንግስት አካል ለውሳኔ መላኩን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ገለፀ፡፡

የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ቤተልሔም ንጉሴ፤ ኢትዮጵያ የራሷ ኮሙዩኒኬሽን ሳተላይት ስለሌላት በአሁኑ ወቅት ከሉግዘመበርግ ኢ ኤስ ኢ ኩባንያ ኢትዮ ሳትን በመጠቀም ላይ ትገኛለች ብለዋል፡፡

ኢትዮ ሳት ኢትዮጵያ ለሳተላይት የምታወጣውን ከፍተኛ ወጪ ከመቀነስ፣ የባህል ወረራን ከመከላከል እንዲሁም ሀገራዊ እሴትን ከማስጠበቅ አንጻር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ኃላፊዋ አንስተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ከ2014 ዓ.ም በአዲስ መልክ የተደራጀው የስፔስ ሳይንስና ጂኢስፓሻል ኢንስቲቲዩ፤ በቀጣይ ኢትዮጵያ የራሷ የኮሙዩኒኬሽን ሳተላይት ባለቤት እንድትሆን የአዋጭነት ጥናት ተጠናቆ ለፕላንና ልማት ሚኒስቴር መላኩንና ውሳኔ እየተጠበቀ መሆኑን ገልጸዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ለኢትዮጵያ መንግሥት ላይ "ውንጀላ አቅርበዋል"፤ "መንግሥት አገሪቱን እንዴት መምራት እንዳለበትም ያልተጠየቁትን ምክር ለግሰዋል" በማለት ወቅሷል‼️

የአምባሳደሩ ንግግር "ትርጉም የማይሰጡ" እና "በበቂ ኹኔታ ያልተጤኑ" ሃሳቦችን ያካተተ ነው ያለው ሚንስቴሩ፣ አምባሳደሩ "በምርጫ የተመረጠውን መንግሥት በኃይል ለመጣል የሚሠሩ ቡድኖችንም በስም ጠቅሰዋል" በማለት ተችቷል። ኢምባሲው፣ በአምባሳደሩ መግለጫ ላይ የተንጸባረቁትን "የፍሬ ነገር ስህተቶች" ለማስተካከል ከኢምባሲው ጋር እንደሚሠራ ገልጧል። አምባሳደር ማሲንጋ ትናንት የመን የማኅበረሰብ ትምህርት ቤት ውስጥ ባደረጉት ንግግር፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደው ጦርነት በሲቪሎች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳይ በመጥቀስ "አገር ዓቀፍ የተኩስ አቁም" እንዲደረግ ጠይቀው ነበር።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
ከ525 ሚሊየን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ‼️

የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ ሊያዙ የቻሉት የሶማሌ ክልል መንግሥት የፀጥታ አካላት፣ የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስ ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል መሆኑ ተገልጿል፡፡

ከተያዙት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መካከልም አልባሳት፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ መድኃኒት፣ ሲጋራ፣ የቤት ክዳን ቆርቆሮ እና ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡

በድርጊቱ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የክትትል ሥራዎች ተጠናክረው መቀጣላቸውን የጉምሩክ ኮሚሽን መረጃ አመላክቷል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
1 ሺህ 147 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ‼️

በዛሬው ዕለት ወደ ሀገር ከተመለሱት 1 ሺህ 147 ዜጎች ውስጥ 1ሺህ 46ቱ ወንዶች፣ 80 ሴቶች እና 21 ጨቅላ ህፃናት መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡

ከሚያዝያ 4 ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ በሚገኘው ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ ከ25 ሺህ 800 በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉን ከሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ
ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ።

https://www.tg-me.com/Poppycarmarket

☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን
ገንዘብዎ ዋጋ የሚያገኝበት ስፍራ!

አያት አክስዮን ማህበር በ2015 ዓ.ም 51% ትርፍ /dividend/ ለባላክሲዮኖች አከፋፍሏል

የ 1 ሚሊዮን ብር አክሲዮን የነበራቸው ባለአክሲዮኖች 510ሺ ብር ትርፍ/Dividend/ አግኝተዋል

የ 5 ሚሊዮን ብር የገዙ 2.5 ሚሊዮን ብር አትርፈዋል

የአንድ አክሲዮን ዋጋ 100 ብር ነው

ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የአክሲዮን መጠን 2500 ነው

ዝቅተኛ የአክሲዮን ዋጋ 262,500 ብር ፣ 5% የአገልግሎት ክፍያን ጨምሮ

112,500 ብር ከፍለው ቀሪውን በሶስት ዓመት መጨረስ ይችላሉ

ከፍተኛ አክሲዮን ገደብ የለውም

አክሲዮኑን ከገዙ ከአንደኛው ወር ጀምሮ የትርፍ ተካፋይ ይሆናሉ

ለበለጠ መረጃ: በ 0910798353/ 0926692990 ይደውሉ ( ቀጥታ ወይም Whatsapp) @ABTrealtor
ሀገሪቷ ከወጪ ንግድ ከ2.5 ቢሊዮን በላይ የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሏ ተገለፀ‼️

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር እንደገለፀዉ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከወጪ ንግድ ከ 2.5 ቢሊየን በላይ የአሜሪከን ዶላር ገቢ መገኘት ችሏል ብሏል።

ሚንስትሩ እንደገለፀዉ በዘጠኝ ወሩ 3.56 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 2.511 ቢሊዮን ዶላር ወይም 70.49 በመቶ ገቢ ማግኘት ተችሏል፡፡

ከተገኘው ገቢ የግብርና ምርቶች 73.6%፣ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ 51.54%፣ ማዕድን ዘርፍ 66.53% እዲሁም ኤሌክትሪክና ሌሎች ምርቶች 71.25% ዕቅድ አፈፃፀም ማሳየት ችለዋል በማለት በሪፖርቱ ገልጿል ።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ክትትል የሚደረግባቸው የቅባት እህሎች፣ የጥራጥሬ ምርቶች፣ የብርዕና አገዳ ሰብሎች፣ የጫት ምርት፣ የቁም እንስሳት እና የደንና ደን ውጤቶች እንዲሁም የቁም እንሰሳት መኖ 811.13 ሚሊዮን ገቢ ለማግኝት ታቅዶ 699.11 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘት ችሏል ማለቱን ካፒታል ዘግቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
2024/05/20 00:03:50
Back to Top
HTML Embed Code: